እንኳን ለልደት በአሉ በሰላም አደረሶት።
ዓመት ጠብቀው ከሚመጡት በአላት አንዱ የገና (ልደት) በአል ነው፡፡ በያመቱ ታኅሣሥ 29 ቀን ይከበራል፡፡ ሃይማኖታዊ ይዘቱ የክርስቶስ ኢየሱስ 2003ኛ የልደት በዓሉ የሚዘከርበት ነው፡፡
በኢትዮጵያ የገና በአል የበአላት ሁሉ በኩር እና ትልቅ የምስራችን ያዘለ በአል ነው። በአገራችን በገና በአል እንደ አቅማችን ዳቦ ደፍተን ጠላ ጠምቀን ንጹህ ለብሰን የገናን በአል ከቤተሰብ ተሰባስበን እናከብራለን።