የስዌን ቆርኪ
ብርቅየው የሰዌን ቆርኪ በኢትዮጵያ ብቻ ከሚገኙት ሰባት ጡት አጥቢ እንሰሳት አንዱ ነው። ቆርኪ ከትከሻው ከፍ ብሎ ከቂጡ ዝቅ ያለ ሲሆን ከአፉም ሾጣጣ ነው። የሰዌን ቆርኪ ከሌሎቹ አገሮች ቆርኪዎች የሚለየው በቀለሙ ነው። ቀለሙም ቸኮሌታማ ሲሆን ከበስተኋላው ነፃ ያለ ነው። ይህ እንሰሳ በአማካኝ የወንዱ ክብደት 150 እስከ 180 ኪሎ ግራም ይደርሳል። ሴቷ ቆርኪ ከወንዱ በመጠን ታንሳለች።







